በቴሌግራም ቴራባይት የብልግና ምስሎችን ያግኙ »

Commercial Bank of Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ commercialbankofethiopian — Commercial Bank of Ethiopia C
የሰርጥ አድራሻ: @commercialbankofethiopian
ምድቦች: ቁማር
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.11K
የሰርጥ መግለጫ

Commercial Bank of Ethiopia is the leading bank in Ethiopia, established in 1942. Pioneer to introduce modern banking to the country with more than 1700 branches across the country.
@ www.facebook.com/combanketh
@ www.twitter.com/combankethiopia

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-02-14 12:05:30 Call for Written Exam
Admin Assistant Applicants for Commercial Bank of Ethiopia
=============

Dear Applicants,

Thank you for your application for the position of Admin Assistant for Commercial Bank of Ethiopia.

We are pleased to invite you to take a written exam on Thursday, February 16, 2023 at 04:00 local time (Morning). 

Note:

• Mobile phone is strictly prohibited; anyone who brings his/her mobile phone will be excluded from the exam.

Please check name lists of applicants to seat for the written exam and place of the exam using the following links:

1. Head Office, Arada, Bole, Kolfe, Megenagna, Merkato, Nifas Silk, Yeka, Ambo and Nekemte Districts Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/AA_University_So_C_514df1144c.pdf

2. Dire Dawa District Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Dire_Dawa_District_1befee45be.pdf

3. Mettu District Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Jimma_District_7d2c37936e.pdf

4. Bahir Dar, Debre Markos and Gonder Districts Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Bahir_Dar_District_1bb8afc8fa.pdf

5. Adama and Assela District Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Adama_District_Office_6d47226582.pdf

6. Debre Berehan District Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Debre_Berehan_District_38be779141.pdf

7. Dila, Hawassa, Shashemene and Robe Districts Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Hawassa_District_cc20241a4f.pdf

8. Dessie, Semera and Woldia Districts Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Dessie_District_fafa0360ad.pdf

9. Hossana and Wolayta Sodo Districts Applicants
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Wolayta_Sodo_District_97cf1252af.pdf
596 views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 12:18:06 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት ሠራተኞች ዝቅተኛ ኑሮ ላላቸው የከተማው ነዋሪዎች የጤና መድህን ዋስትና ገዝተው አበረከቱ፡፡
==================================

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት ጽ/ቤት ስር የሚገኙ ሠራተኞች እና የሥራ አመራት አባላት ከደሞዛቸው ላይ በማዋጣት በጎንደር ከተማ አስተዳደር ፋሲል እና ማራኪ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው 54 ነዋሪዎች የጤና መድህን ዋስትና ሽፋን እንዲያገኙ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት ቅጥር ግቢ ውስጥ በተደረገ ሥነ-ሥርዓት  የጤና መድህን ዋስትናው ለክፍለ ከተሞቹ የሥራ ኃላፊዎች ተሰጥቷል፡፡ በዚሁ ጊዜ የዲስትሪክቱ ዳይሬክተር አቶ ደመወዜ ባልቢ እንዳሉት የባንኩ ሠራተኞች ከደሞዛቸው በማዋጣት በየአመቱ ለተወሰኑ አነስተኛ ገቢ ላላቸው የከተማው ነዋሪዎች የጤና መድህን ዋስትና ለመግዛት እና ለማደስ የሚያደርገው እገዛ ቀጣይነት ያለዉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት ሠራተኞች እና የአመራር አባላት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ረገድ ለሌሎችም አርዓያ መሆን የሚችል ተሞክሮ ያላቸው ሲሆን፣ በደስታም ሆነ በችግር ጊዜያት የማህበረሰቡ አጋር መሆናቸውን በተግባር ማሳየታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
1.9K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 16:54:49 በ EthioDirect
ባሉበት ምቾትዎ እንደተጠበቀ በሞባይል ስልክዎ አማካኝነት ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ ይችላሉ!
#ፈጣን #ቀላል #ነፃ #አስተማማኝ
=============
EthioDirect መተግበሪያ (Application) ለማውረድ፡
•  ለአንድሮይድ ስልኮች፡- https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
•  ለአይፎን ስልኮች፡- https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491
426 views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 16:54:37 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በትግራይ ክልል አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ቅርንጫፎች 64 መድረሳቸውን አስታውቀዋል፡፡
******
አቶ አቤ በትዊተር ገፃቸው እንዳስታወቁት ደንበኞች ከማንኛውም ቅርንጫፍ ሂሳባቸውን ማንቀሳቀስ የሚችሉበት አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን፣ የኔትዎርኩ ሁኔታ አስተማማኝ ሲሆን እና የደንበኞች መረጃ ትክክለኛነት ሲረጋገጥ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች በአፋጣኝ የሚጀምሩ ይሆናል፡፡

https://twitter.com/AbieSano
428 views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 16:54:19 መነሻ
====
ወ/ሮ ሳምራዊት ሞገስ የትራቭል ኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅት ባለቤት ናቸው፡፡

ወ/ሮ ሳምራዊት የአስጎብኚ ድርጅታቸውን መስርተው አሁን ለደረሰበት ስኬት ለማብቃት በብዙ ፈተናዎች ማለፍ ነበረባቸው፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአስጎብኚ ድርጅታቸው ከ50 በላይ ሠራተኞችን ቀጥረው በማሰራት ላይ የሚገኙት ወ/ሮ ሳምራዊት ወደዚህ ሥራ ከመግባታቸው በፊት እራሳቸውም የመንግስት ሥራ ተቀጣሪ ነበሩ፡፡

ወ/ሮ ሳምራዊት ለባንካችን የቴሌቪዥን ዝግጅት ክፍል ካስተዳደጋቸው ጀምሮ አሁን እስከደረሱበት ደረጃ ድረስ ያለውን ረዥሙን የህይወት ልምዳቸውን ባካፈሉበት ቆይታ ለስራቸው መቃናት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያደረገውን አስተዋፅኦም አንስተዋል፡፡

ከዝግጅቱ ብዙ ይማራሉና እንዲመለከቱት ጋብዘናል፡፡



383 views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 16:53:43 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ በርካታ ተጨማሪ ቅርንጫፎች የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
***********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ ክልል በሽሬ፤ አክሱም፤ ዓድዋ፤  ሰለኽለኻ፤ ማይ ፀብሪ፤ እንዳባጉና፤ ውቕሮማራይ፤ ዓዲግራት፣ ውቕሮ፣ ፍረወይኒ፣ ሓውዜን፣ ዓዲጉዶም፣ ሒዋነ፣ ዓዲሽሁ፣ መኾኒ፣ ማይጨውና አካባቢው በሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎች የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

የኢትዮጰያ ንግድ ባንክ አገልግሎት መስጠት በጀመረባቸው ቅርንጫፎች ለደንበኞች የተሟላ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የባንኩ ደንበኛ የሆነ ማንኛውም ሰው በየትኛውም የሃገሪቱ ክፍል የከፈተውን የሂሳብ ደብተር ይዞ በመቅረብ አገልግሎት ማግኘት ይችላል፡፡

በተለያየ ምክንያት የሂሳብ ደብተራቸው የጠፋባቸው ደንበኞች ካሉ መታወቂያቸውን ይዘው በመቅረብ ባንኩ ከዚህ ቀደም ይጠቀምበት በነበረ አሰራር መሰረት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ከመቐለ ዲስትሪክት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመቐለ ከተማ በሚገኙት ሁሉም ቅርንጫፎች እንዲሁም በዓብይ ዓዲ፤ ማይ ለሚን፤ ሳምረ፤ ግጀት፤ ሃይቂ መስሓል፤ወርቅ አምባ፤ አፅቢ እና አጉላዕ እና በሌሎች አካባቢዎች በሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎች በትናንትናው ዕለት የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ይታወሳል፡፡
439 views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 19:50:21 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተቀማጭ ገንዘቡን ከ1 ትሪሊየን ብር በላይ በማድረስ ላስመዘገበው ትልቅ ስኬት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ እንደነበር ተገለፀ፡፡
********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የባንኩ የተቀማጭ ገንዘብ ከ1 ትሪሊየን ብር በላይ መሻገሩን በማስመልከት በተዘጋጀ የምስጋና መርሀ ግብር ላይ እንደተናገሩት የተገኘው ስኬት የደንበኞች፣ የሰራተኞች፣ የአመራሮች፣ የዳይሪክተሮች ቦርድ አባላት፣ የመንግስት እና የሌሎች ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ውጤት ነው፡፡

አቶ አቤ የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ የባንኩን የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በእጥፍ በማሳደግ ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ለማድረስ ሁሉም በአንድ ልብ ሊሠራ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በሁሉም ደረጃ የሚሠራው ስራ ባንኩን ወደተሻለ ምእራፍ የሚያሸጋግር ነው ያሉት የቅርንጫፍ እና ሪቴይል ባንኪንግ ኤክስኪውቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ፍቀረስላሴ ዘውዱ በበኩላቸው ለበለጠ ውጤት ሁሉም የባንኩን ራእይ ሰንቆ ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙ የባንኩ ዲስትሪክት ጽ/ቤት ዳይሬክተሮች የተገኘው ስኬት የቅርንጫፎች የስራ ውጤት መሆኑን ገልፀው ለዚህም ሠራተኞች ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሠራተኞች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ኦላኒ ሳቀታ የባንኩን ሠራተኞች በመወከል ባስተላለፉት መልእክት የዚህ ታሪክ አካል በመሆናችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል፡፡
2.7K views16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 22:34:19 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ ክልል  የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
***********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትግራይ ክልል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የባንክ አገልግሎት በዛሬው እለት ድጋሜ አስጀምሯል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከብሄራዊ ባንክ  ለክልሉ የተላከውን ብር ለቅርጫፎች በማከፋፈል  በመቐለ ከተማ በሚገኙት ሁሉም ቅርንጫፎች እንዲሁም በዓብይ ዓዲ፤ ማይ ለሚን፤ ሳምረ፤ ግጀት፤ ሃይቂ መስሓል፤ወርቅ አምባ፤ አፅቢ እና አጉላዕ በሚገኙ በአጠቃላይ በ31 ቅርንጫፎች የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

በተጨማሪም በዓዲግራት፣ ውቕሮ፣ ፍረወይኒ፣ ሓውዜን፣ ዓዲጉዶም፣ ሒዋነ፣ ዓዲሽሁ፣ መኾኒ፣ ማይጨውና አካባቢው በሚገኙ ቅርንጫፎች  በቅርብ ሰዓታት ውስጥ  ባንኩ የተሟላ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ከመቐለ ዲስትሪክት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የኢትዮጰያ ንግድ ባንክ ሥራ የጀመረባቸው አካባቢዎች የቴሌ መሰረተ ልማት ዝርጋታዎች የተሟላባቸው ሲሆን፣ የተወሰኑ የቴሌ መሰረተ ልማት ጥገና  ባልተጠናቀቀባቸው አካባቢዎች በቅርቡ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁ ተገልጿል፡፡
927 views19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 01:46:17
4.4K views22:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 14:18:27
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ‘ኢትዮ ዳይሬክት’ (EthioDirect) የተሰኘ ዲጂታል የውጪ ሐዋላ አገልግሎት መስጫ ፕላትፎርም ጥቅም ላይ አዋለ፡፡
============================

አገልግሎቱን  በይፋ ስራ ለማስጀመር በተዘጋጀ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንዳሉት ወቅቱን ያገናዘበ ዲጂታል የገንዘብ መላኪያ ዘዴን ተግባራዊ ለማድረግ ፕላትፎርሙ ጥቅም ላይ እንዲውል መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ደንበኞች ‘EthioDirect’ መተግበሪያን ከፕሌይ ስቶር እና አፕስቶር በማውረድና ሞባይል ስልካቸው ላይ በመጫን ከውጪ ሀገራት ወደ ሀገር ውስጥ ገንዘብ መላክ እንደሚችሉ የተገለፀ ሲሆን፣ በቀጣይ በ https://www.ethiodirect.com ድረ ገጽ አገልግሎቱ እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡

መተግበሪያው ደኅንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ መሆኑን የተናገሩት አቶ አቤ፣ ደንበኞች ምቾታቸው እንደተጠበቀ በማንኛውም ጊዜና ቦታ  ከክፍያ ነፃ ሐዋላ መላክ የሚችሉበት ዘመናዊ አገልግሎት መስጫ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ደንበኞች እንደ ማስተርካርድ እና ቪዛ የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርዶችን በመጠቀም በመተግበሪያው ገንዘብ መላክ የሚችሉ መሆኑን የገለፁት አቶ አቤ፣ የሚላከው ገንዘብ በቀጥታ ወደ ተቀባዩ የባንክ ሒሳብ የሚገባ ሲሆን በቀጣይ ወደ ሲቢኢ ብር ዋሌት ማስገባት ወይም ተቀባዩ በአቅራቢያው ከሚገኝ የባንክ ቅርንጫፍ እንዲቀበል ለማስቻል ይሰራል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጪ ምንዛሬ በመሰብሰብ ለተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የማቅረብ ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት እንዳለበት ይታወቃል ያሉት አቶ አቤ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝቱን ለማሳደግ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን ነድፎ በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
4.6K views11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ