2023-01-15 20:19:32
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “ድንቅ ምድር” በሚል መሪ ቃል በአማራ ክልል ቱሪዝም ቢሮ የተዘጋጀውን የቱሪዝም የዕውቅና እና የሽልማት መርሃ ግብር በፕላቲኒየም ደረጃ ብቸኛ አጋር መሆኑ አስታወቀ። ==========================================
በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ከ80 ዓመታት በላይ የዘለቀው እና በዘርፉ በመሪነት የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማኅበራዊ ሓላፊነትን በመወጣት ረገድም ግንባር ቀደም የሕዝብ አጋርነቱን ሲያረጋግጥ ቆይቷል፡፡
ባንኩ በዚህ ወቅት በአማራ ክልል ደረጃ ብቻ እንኳ በስድስት የዲስትሪክት ጽ/ቤቶች ሥር በክልሉ የተሰራጩ በርካታ ቅርንጫፎችን ከፍቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን፣ ከክልሉ መንግሥት እና ከሌሎች አካላት ለሚቀርቡ የስፖንሰርሺፕ እና የድጋፍ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ይታወቃል፡፡
ለዚህ አንዱ ማሳያ ደግሞ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ “ድንቅ ምድር” በሚል መሪ ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደውን የቱሪዝም የዕውቅና እና የሽልማት ፕሮግራም በፕላቲኒየም ደረጃ በብቸኛ አጋርነት መደገፉ ነው፡፡
የቱሪዝም ዘርፉ በውጭ ምንዛሬ ምንጭነት፣ ለሌሎች ዘርፎች ገበያ በመፍጠር፣ ሕዝቦችን በማቀራረብ እንዲሁም ለጠቅላላ ብሔራዊ ምርት እድገት ከፍተኛ ሚና ስለሚጫወት መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት እንደሰጠው ይታወቃል፡፡
የአማራ ክልል ደግሞ በዩኔስኮ ከተመዘገቡ ዘጠኝ ቋሚ የኢትዮጵያ ቅርሶች መካከል የሦስቱ እንዲሁም የበርካታ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ የቱሪዝም ሀብቶች መገኛ በመሆኑ፣ ለሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ ልማት እና አስተዋፅኦ የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል።
ስለዚህም የዕውቅና እና የሽልማት ፕሮግራሙ በቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን ለማበረታታት፣ በኮቪድ-19 እና በሰላም እጦት ምክንያት የተቀዛቀዘውን የክልሉን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ለማነቃቃት፣ የክልሉን የቱሪዝም ጸጋዎች ለማስተዋወቅ እና ለሌሎችም ገንቢ ዓላማዎች ይካሄዳል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም የፕሮግራሙ ዋና አጋር በመሆን ማኅበራዊ ሓላፊነቱን ሲወጣ ፕሮግራሙ ለክልሉ ብሎም ለሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በማመን ነው፡፡
1.4K views17:19