2022-08-30 23:18:10
ይታየኛል፡፡ ልቤ ሲረግብ ተሰማኝ፡፡ ከጀርባው ነው አመጣጤ፤ አጠገቡ ስደርስ ስልክ እንደያዘ ዐየሁ፡፡ ቆም አልኩ፡፡
“ተይ ባክሽ...! ምን የመሰለች ጅራታም ኮከብ ዐየሁ መሰለሽ አሁን ግን ካንቺ አይበልጥም….. ካንቺ ቂጥ የሚበልጥ ቂጥ የለም!" ሲል ሰማሁት፡፡
ውሃ ልኬ የተዛባ መሰለኝ፡፡ አውላላ አስፋልት ላይ፣ በጠራራ ፀሐይ፤ በቂጤ ዝርፍጥ ልል ምንም አልቀረኝ፡፡ ተንገዳገድኩ፡፡ ድንጋጤ አይደለም፡፡
_________
ለዓመታት ፍቅሩን የሚጫረቱኝ ሴቶች እንዳሉ ዐውቃለሁ፡፡ ሻሞ
ውስጥ እንደምሳተፍም ይገባኛል፡፡
አንዳንዴም ትራፊው እንደሚደርሰኝ፤ እንጥፍጣፊው፣ ያለቀበቱ እንደሚመጣልኝ ዐውቃለሁ፤ ይሄኛው ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ መሰለኝ፡፡
ላለመወሰን መፍራትን ማቆም መሰለኝ፡፡ የተደበቀው በአደባባይ ሲታይ፤ ሰው እየሰማው እንዲህ ሲል፤ ለመያዝ የፈለገ፣ የእኔን “ሂድ በቃ” ሽኝት የጠየቀ መሰለኝ፡፡
ላለመሰማት፣ ላለመያዝ መሞከሩን ያቆመ መሰለኝ፡፡ ሰምቼ ሂድ እንድለው፡፡ ቆርጦልኝ እንዳሰናብተው፡፡ እንጥፍጣፊውንም ሊነፍገኝ፣ ያለቀበትንም ሊከለክለኝ የወሰነ መሰለኝ፡፡
ያ መሰለኝ ያሸበረኝ፡፡ ያ መሰለኝ ያናወጠኝ፡፡
ስሜቴን በቅጡ ሳላስተናብር አጠገቡ ደርሼ ተቀመጥኩ፡፡
“እሺ… እደውላለሁ በኋላ…” ወይም ይሄን የሚመስል ነገር ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡
ይወዳቸው በነበሩት ዐይኖቼ ዐየሁት፡፡ ሌላ በሚያዩ ዐይኖቹ ዐየኝ፡፡
እንደሰማሁ አውቋል፡፡ ግን አልደነገጠም፡፡ ግምቴ ልክ ነበር፡፡
በደም ስሬ፣ ደም ሳይሆን የበረዶ ውሃ የሚሄድ ይመስል ያንሰፈስፈኝ ጀመር፡፡ ዘፋኙ፣ “እትት በረደኝ በረሃ ላይ ቆሜ” ያለው እንዲህ ያለው ነገር ደርሶበት መሆን አለበት፡፡ _
“ኤፊ…” አልኩ ያለኝን ጉልበት አስተባብሬ፡፡
“እ…”
ልብ አድርጉልኝ፣ “ወዬ” ዎቹ፣ “ወይ ማርዬ”ዎቹ፣ “ምን አልሽኝ የኔ ቆንጆዎቹ፤ በ “እ…” ከተተኩ ኑ ወራት አልፈዋል፡፡
“እ….” ይለኛል ዝም እንዳይለኝ፡፡ አለሁምም፤ የለሁምም ነገር ነው፡፡
“እ…” አባባሉ፣ እሰማለሁም፤ አልሰማምም ነገር፡፡
“ከሌላ ሴት ፍቅር ይዞሃል?”
“እ?”
“ሌላ ሴት ወደሃል ወይ?
_ ዝም፡፡
መልሱን አውቀዋለሁ፡፡
633 views20:18