2022-08-01 13:26:44
ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ!
......(( ክፍል 5))......
=====================
@Raymondds የተፆፈ በRaymond
ተዘጋጅቶ የቀረበ
መልካም ንባብ
ወደ ክፍሉ ጠጋ ብዬ ሳዳምጥ ድምፁ ጥርት ብሎ እየተሰማኝ
መጣ........ገርበብ ባለው በር ሾከክ ብዬ ሳሾልቅ እኔን
የሚያካክሉ ሴት ህፃናት ሲጫወቱ አየሁ። በሩን ገፋ አደረኩት።
ክፍሏ ውስጥ ከሆነ ጊዜያት በፊት እንደኔ አመዳምና ቀጫጫ
የነበሩ የሚመስሉ አሁን ግን ወዛቸው መለስ ብሎላቸው እንደ
ቅንጥሽ ለመመጠጥ የደረሱ አምስት እኩዮቼ ሲያዩኝ ከልባቸው
በሆነ ደስታ እየተሯሯጡ ተቀበሉኝ። በሩን ዘግተው ልክ ሰው
ተርበው እንደከረሙ ሁሉ ከአፌ ቃላት እስኪወጣ ድረስ ቁልጭ
ቁልጭ እያሉ ይመለከቱኛል። ሁሉም ስማቸውን አስተዋወቁኝ
በአሁኑ ሰዓት ሶስቱ ሴቶች ስም ያላቸው ዝነኞች ስለሆኑ
ስማቸውን አልነግርህም''
" ችግር የለውም ሪችዬ.....አንቺ መናገር የምትፈልጋውን
ታሪክሽን ብቻ አጫውቺኝ" አልኳት። አሁን ጫቷን ጨርሳ
ቩቩዜላዋን((ሺሻዋን)) እየነፋች ነው።
"እሺ ወንዴ ምን ላይ ነበርኩኝ?" አለችኝ። ምርቅን ስላለች አሁን
ያወራችውን ስለረሳችው ምንም አልገረመኝም
" ህፃናቶቹ....."
"አዎ........እዛ ክፍል ውስጥ ያገኘኋቸው ህፃናት እኔን
በማየታቸው ደስ የተሰኙ ይመስላሉ......ስሜን ፣ ከየት
እንደመጣሁ ጠየቁኝ.....እውነቱን ነገርኳቸው። እነርሱም
ስማቸውንና የህይወት ታሪካቸውን አንድ ባንድ ነገሩኝ። ሁሉንም
እንደ'ኔ የኑሮ ቦክስ ደቁሷቸዋል። ታሪካቸውን ከነገሩኝ ልጆች ግን
እስከዛሬ ድረስ የማልረሳው ያሚ እያልን የምንጠራት ልጅ
የነገረችኝን ነው.......አሁን በህይወት የለችም ነፍሷን
ይማረውና.........ምን እንዳለችኝ ታውቃለህ?......ለሁለት
አመታት ሙሉ አባቷና ታላቅ ወንድሟ በጋራ ሆነው ሲደፍሯት
ኖረዋል። በዚህ የተነሳ ያሚ ጭንቀታምና ፈሪ ነበረች።........ያን
ጊዜ የsex ጣዕም ባይገባኝም ፣ የመደፈርን ስቃይ ያን ያህል
ጠልቄ ባላውቀውም ታሪኳ ግን ልቤን ነክቶኝ "አዎ........እዛ
ክፍል ውስጥ ያገኘኋቸው ህፃናት እኔን በማየታቸው ደስ የተሰኙ
ይመስላሉ......ስሜን ፣ ከየት እንደመጣሁ ጠየቁኝ.....እውነቱን
ነገርኳቸው። እነርሱም ስማቸውንና የህይወት ታሪካቸውን አንድ
ባንድ ነገሩኝ። ሁሉንም እንደ'ኔ የኑሮ ቦክስ ደቁሷቸዋል።
ታሪካቸውን ከነገሩኝ ልጆች ግን እስከዛሬ ድረስ የማልረሳው ያሚ
እያልን የምንጠራት ልጅ የነገረችኝን ነው.......አሁን በህይወት
የለችም ነፍሷን ይማረውና.........ምን እንዳለችኝ
ታውቃለህ?......ለሁለት አመታት ሙሉ አባቷና ታላቅ ወንድሟ
በጋራ ሆነው ሲደፍሯት ኖረዋል። በዚህ የተነሳ ያሚ ጭንቀታምና
ፈሪ ነበረች።........ያን ጊዜ የsex ጣዕም ባይገባኝም ፣
የመደፈርን ስቃይ ያን ያህል ጠልቄ ባላውቀውም ታሪኳ ግን
ልቤን ነክቶኝ ነበር።
ከዛ ያው ልጆች አይደለን?ጥቂት ቆይተን ብሶታችንን ረስተን
መጫወት ፣ መንጫጫት ፣ መዝለል ጀመርን። ታዲያልህ በዛን
ወቅት ሁላችንም ለምን እዚህ ቤት ውስጥ እንደመጣን
የምናውቀው ነገር አልነበረም። ብቻ ባሻን ሰዓት የፈለግነውን
እንበላለን ፣ እንለብሳለን ፣ በሳምንት አንዴ ከሞግዚታችን ጋር
ሆነን ከግቢ እየወጣን እንዝናናለን። ነገር ግን ያለንበት ግቢ
ውስጥ እስካለን ድረስ ከ1ኛው ፎቅ ውጪ ወደላይም ሆነ
ወደታች መውረድ አይፈቀድልንም ነበር። እኔ ደግሞ እድሜ
ልኬን በነፃነት ጎዳና ላይ ያደኩ ልጅ በመሆኔ ነፃነቴን መነፈጌ
ሸክኮኛል። አንድ ቀን ይሄንን የቤቱን ህግ እንደምጥሰው
እርግጠኛ ነኝ እያልኩ ለሳምንታት አሰላስል ነበር። ነገር ግን
የሚገጥመኝን ቅጣት ስላላወኩ ድፍረቱን አጣሁኝ።
ከዕለት ወደ ዕለት የእኔም የህፃናቶቹም ሰውነት እየፋፋ መጣ ፤
የእያንዳንዳችን ውበት ቁልጭ ብሎ መታየት ጀመረ። ውበታችን
እንደ ሉባንጃ እጣን ለማንም መሽተት ሲጀምር ያቺ ድብልብል
ሴትዮ ከሆነች ፓውደራም ሴትዮ ጋር መጣችና
"ከነገ ጀምሮ የዳንስ ትሬዲንግ ትጀምራላችሁ ፣ አሰልጣኛችሁ
ደግሞ እሷ ናት" አለችን። እንደተባልነውም ስትሪፕ ቤቶች
ውስጥ የሚደነሱ ዳንሶችን የብረት ዘንግ ላይ እየተንጠላጠልንና
እየተፋተግን መሰልጠን ጀመረን። ሁላችንም እንደጨዋታ
ስለምንቆጥረው የዳንስ ስልጠናውን በጣም እንወደው ነበር።
ቅድም እንዳልኩህ በሳምንት አንድ ቀን ሽርሽር እንሄድ የለ?"
"አዎ"
"ታዲያልህ አንድ እሁድ ቀን ከሞግዚታችን ጋር ሆነን አንበሳ ግቢ
ግምታም የሆኑ አንበሶችን በአይናችንም በአፍንጫችንም
ጎብኝተን ስንመጣ ልክ ቅድስተ ማርያም ጋር ስንደርስ
መኪናችንን ትራፊክ አስቆመው። ማርያምን ልሳለም ዞር
ስል......ያ ሸንካላ አባቴ እግሩን ክራንች ላይ ሰቅሎ ሲለምን
አየሁት። ሰውነቴን በሙሉ ነዛዘረኝ። ሳላስበው 'እንዴ!!!!' ብዬ
ጮህኩኝ። ሞግዚታችን ምን እንደሆንኩ ጠየቀችኝ።.....'ያ' ብዬ
ወደ አባቴ ጠቆምኳት.......ሸንካላው አባቴን አየችና ከንፈሯን
እየመጠጠች "ጋሽ ድንቁን ነው?" አለችኝ። ጊዮርጊስን ነው
የምልህ! እስከዛች ቀን ድረስ የአባቴን ስሙን አላውቀውም
ነበር። ምክንያቱም አንደኛ ፍላግቱ አልነበረኝም ሁለተኛ ሌሎች
የኔ ቢጤዎችም የሚጠሩት በስሙ በሚለምንበት መንግስቱ ሀ/
ማርያም እያሉ ነበር።
ሞግዚቷ ግን አባቴን የት እንደምታውቀው ግራ ገባኝ.....
"የት ነው የምታውቂው?" አልኳት
"ምስኪን የኛ ቤት ደንበኛ ነበር" አለችኝ። ልክ ይሄ ቃል ከአፏ
ሳታስበው እንደወጣ ሁሉ ከነገረችኝ በኋላ ስትደነግጥ
አስተዋልኩ።
"የኛ ቤት ደንበኛ ነበር ነው ያልሽው? እንዴት? አልገባኝም?"
የጥያቄ መአት አዥጎደጎድኩባት። እርሷ ግን ወስፌ ከለገመ
ቅቤ አይሰፋም እንዲሉ አንዲት ቃል እንኳን አልተነፍስ አለችኝ።
እኔ ግን የአባቴ ነገር ለቀናት ራስ ምታት ሆነብኝ። ርገጠኛ ነኝ
እኔ ራስ መኮንን ወንዝ ስር አግኝቼ የሰጠሁት መስቀል የወርቅ
ይመስለኛል። ስለሆነም ነው ገንዘብ ሲያገኝ ትቶኝ የጠፋው።
ታዲያ ብሩን የት አጥፍቶት ነው? በአረቄና በጠጅ ብቻ በዚች
ጥቂት ወራት ውስጥ እርግጠኛ ነኝ አይጨርሰውም! ታዲያ
እንዴት አለቀለት? ነው ወይስ እሱም እንደ አንዳንድ የኔ
ቢጤዎች ብሩን ቀክሮ ልመና ሱስ ሆኖበት እየለመነ ነው? ብዙ
የኔ ቢጤዎች በህመምና በረሀብ ተሰቃይተው ሲሞቱ ትራሳቸው
ስር አርባና ሀምሳ ሺ ብሮች ሲገኝባቸው አይቻለሁ። እንደውም
አንድ ጊዮርጊስ ጋር ይለምን የነበረ ሽማግሌ ሰውዬ ሲሞት
የላስቲክ ዳሱ ውስጥ በደርግ ዘመን የነበረ ብር ብቻ ወደ ሀያ ሺ
ብር ተገኝቶበት የአንድ ሰሞን የመፅሔትና የጋዜጣ ዜና ሆኖ
ነበር።
ሞግዚታችንስ የኛ ቤት ደንበኛ ነበር ስትል ምን ማለቷ ነው?
እዚህ ያለሁበት ቤት ውስጥስ ምን የሚሸጥ ነገር ኖሮ ነው እሱ
ደንበኛ የነበረው?
ሁሉ ነገር ጨቅላው አእምሮዬ ከሚያስበው በላይ ስለሆነብኝ
በውጥረት ልፈነዳ ደረስኩኝ። ለሁለት ቀናት ያህል ከህፃናቶቹ
ርቄ ብቻዬን ከክፍሌ ሳልወጣ አሳለፍኩኝ። ብቻዬን አንድ ክፍል
ውስጥ ታሽጌ ስለሱ ማሰቤ ኡኡ እስክል ድረስ
አሳበደኝ።.....ወንዴ.....ይሄን ያህል ያሳሰበኝ አዝኜለት
64.3K views10:26