Get Mystery Box with random crypto!

ISLAMIC SCHOOL 2

የቴሌግራም ቻናል አርማ loveyuolema — ISLAMIC SCHOOL 2 I
የሰርጥ አድራሻ: @loveyuolema
ምድቦች: የአዋቂዎች ይዘት (18+)
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.87K
የሰርጥ መግለጫ

✍ ጅልከሆንክ ጅል ተከታይ ጀንትል ከሆንክ አስከታይ ትሆናለህ..!
ጅልም ጀንትልም ካልሆንክ ደግሞ አርፈህ በራስህ ዓለም ትኖራለህ..! አንባቢ እንሁን፡፡ለውጥ ከራስ ቢጀመር ...የቸገረን ጥሩ መካሪ ሳይሆን፤
የሰማነውን መተግበር ነው ያቃተን!ጅህልና በሽታ ነዉ፡፡
🎖For any comment
T.me/Anws_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 20:55:39   ሰይድ አቡበክር ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው
«ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም
ዑመር ትንሽ ቆይተው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ሲገቡ አቡበክር አጠገባቸው እንደተቀመጡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በጣም ተቆጥተው ፊታቸው ቀልቶ አዩዋቸው።

   አቡበክርም ይህንኑ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሁኔታ ሲመለከቱ
ያበርዷቸውና ያረጋጓቸው ጀመር፡፡ «ረሱል ሆይ! እባክዎን ይረጋጉ እኔ ነኝ ጥፋተኛ አሉ። ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “ምን ሆነህ ነው ዑመር እንዴት ለአቡበክር ፊት ትነሳዋለህ?..»

   "ሰዎች ሆይ! ይህን ዲን ዤ ስመጣ ሰው ሁሉ ፊት ሲነሳኝ
የተቀበለኝ አቡበክር ነው፡፡ እውነተኛ ነህ ያለኝ አቡበክር ነው፡፡ ገንዘቡን፣ ነፍሱንና ቤተሰቡን አሳልፎ የሰጠኝ አቡበክር ነው፡፡ እባካችሁ ጓደኛዬን እንዳትነኩት፡፡" ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አቡበክርን(ረ.ዐ) ቀና ብሎ ያያቸው ኣልነበረም፡፡

           የመዋደድ ውበት

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና በአቡበክር(ረ.ዐ) መካከል የነበረው መዋደድ መለኪያ አልነበረውም። አንድ ቀን በነብዩና (ሰ.ዐ.ወ) በእሜቴ ዓኢሻ መካከል የፍቅር ጭቅጭቅ ይጀመራል፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ «በመካከላችን ማን እንዲፈርድ ትፈልጊያለሽ፡፡ አቡ ኡበይዳ ይፍረድ?›› ዓኢሻም “አቡኡበይዳ መልካም ሰው ቢሆንም ከመጣ እርሶን ነው የሚደግፈው” ይላሉ ‹‹እሺ አባትሽ ይሁን?› እሜቴ ዓኢሻ ይስማማሉ፡፡

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አስ-ሲዲቅን አስጠሯቸው። አቡበክር እንደመጡ እሜቴ እንዲህ ይላሉ «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እውነቱን ብቻ
ይንገሩት›› አቡበክርም ተቆጥተው ‹‹እርሳቸው ያለእውነት መች ይናገራሉ” ብለው ዓኢሻን ሊመቷት ተጠጉ፡፡ ረሱልም (ስ.ዐ.ወ)
በመሃላቸው ይገቡና ‹‹አቡበክር ይህን እንድታደርግ አላስጠራንህም፡፡ በቃ ተወው›› ይሏቸዋል፡፡

  አቡበክር ከወጡ በኋላ ለእሜት ዓኢሻ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ
ይሏቸዋል «በእርሱና በአንቺ መካከል እንዴት ገላጋይ እንደሆነኩ አየሽ አይደል» አቡበክር(ረ.ዐ) ቆየት ብለው ተመልሰው ሲገቡ ሁለቱም ሲሳሳቁ አገኙዋቸውና ‹‹ስትፋለሙ እንደጠራችሁኝ በተስማማችሁ ጊዜም አሳትፉኝ» በማለት ቀለዷቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «አቡበክር ና ተሳተፍ› አሏቸው፡፡

  ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውደድ ከአላህ (ሱ.ወ) የሚገኝ በረከትና ጸጋ
ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ባሪያውን ሲወድ ይህን በረከትና ጸጋ ያጎናጽፈዋል፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወደድክ ማለት የአላህን (ሱ.ወ) ሪዝቅና ችሮታ አገኘህ ማለት ነው፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወዳጆች ከሆኑ ሙስሊሞች ጎን መሰለፍም ይጠበቅብናል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሌሊት ጉዞ ባደረጉበትና ወደሰማይ በመጠቁበት ወቅት የአፍታ ማረፊያ የነበራቸው ቁዱስን ከጥቃት ካልተከላከልን
እንዴት ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) እንወዳለን እንላለን፡፡ ታላቁ አቡበክር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከእንቅልፋቸው እንዳይነቁ ብለው እባብን የሚያክል ነገር
ሲነድፋቸው ድምጻቸውን ዋጥ ማድረጋቸዉን አይተናል፡፡ እኛ ግን የተቀደሰ የመሰሊም ግዛቶች በጠላት እጅ ሲቆሽሹ ዐይተን እንዳላየ
መስለን እናንቀላፋልን፡፡

  አንድ ቀን አቡበክር(ረ.ዐ) ለረቢዓ ቢን ካዕብ ትንሽ የሚያስከፋ ንግግር ይናገሩትና በመካከላቸው አለመግባባት ይፈጠራል፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) በሁኔታው ያዝኑና «ረቢዓ ግድ የለም የተናገርኩህን መልሰህ ተናገረኝ” ይሉታል፡፡ ‹‹ረቢዓም መልስማ አልሰጦትም» ይላል፡፡ አቡበክርም «ረቢዓ በዚህ ንግግሬ አላህ ፊት እንድከሰስ ትፈልጋለህ?›› ይሉታል፡፡ ሳይናገር ዝም ይላቸዋል፡፡ አቡበክርም ቆጣ ብለው «ከዚህ ቃሌ ጋር አላህ ፊት እንድቀርብ ትወዳለህ ማለት ነው ወላሂ ለረሱል ሄጄ እነግራቸዋለሁ» ይላሉ፡፡

  የረቢዓ(ረ.ዐ) ወገኖችም ተገርመው «ራሱ የሚያስከፋ ንግግር ተናግሮህ ሲያበቃ እንደገና ለረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እናገራለሁ ይላል እንዴ?›› ይላሉ። ሪቢዓም «ለመሆኑ የሰውየውን ማንነት አውቃችኋል? ዝም በሉ አስ-ሲዲቅ እኮ ነው! አሁን ለኔ ወግናችሁ እንዲህ ስትናገሩ እንዳይሰማንና እንዳይቆጣን ደግሞ! ከተቆጣ ለረሱል ሄዶ ይናገራላ ረሱልም እርሱን በማስቆጣታችን ይቆጡናል እርሳቸው ከተቆጡ ደግሞ ለእርሳቸው እና ለአቡበክር ቁጣ ሲል አላህም ስለሚቆጣ ረቢዓን ታስጠፋላችሁ፡፡ አሁን ዝም በሉ፡፡››ይላቸዋል ረቢዓ(ረ.ዐ) በስጋት ከአስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ኋላ እየተከተለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሲደርሱ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ ብለው "አል ሲዲቅና አንተ ምን ሆናችሁ?" ይላሉ አንድ የሚያስከፋኝን ቃል ተናገሩኝና እርሱን መልሰህ ተናገረኝ ሲሉኝ እኔ ደግሞ አይሆንም አልኳቸው›› አለ ረቢዓ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «ረቢዓ አዎን ልክ ነህ፡፡ ከአቡበክር ጋር መመላለስ የለብህም ይልቁንም አቡበክር ሆይ! አላህ ይማርህ» ብለው» አሉት፡፡

              በስንብቱ ዋዜማ

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስልሣ ሶስተኛ ዓመታቸው ላይ ደርሰዋል፡፡
ሠውነታቸው ላይ የድካም ሁኔታ ይተይባቸው ጀምሯል። አንዲት ሴት ወደ ርሳቸው ዘንድ መጥታ የሆነ ነገር እንዲሰጥዋት ጠይቃቸዋለች፡፡ ከዓመት በኋላ እንድትጠይቃቸው ይነግሯታል፡፡ እርሷም «እኔ ስመለስ ባላገኞትስ?›› ትላለች፡፡ ከመድከማቸው የተነሳ እስከ ቀጣዩ ዓመት ሊቆዩ እንደማይችሉ ገምታለች። «እኔን ካላገኘሽኝ አቡበክር ጋር ሄደሽ ትጠይቂዋለሽ ይሏታል። ይህ የመልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) አባባል ከርሳቸው በኋላ አቡበክር እንደሚተካቸው (ሊተኳቸው እንደሚገባ) አመላካች ነው፡፡

  ከዚህ ክስተት በኋላ ነበር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የመሰናበቻውን ሐጅ
ያደረጉትና ተከታዩ የቁርዓን አንቀጽ የወረደው

الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا ۚ

"ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡"  (ሱረቱል ማኢዳህ- 3)

  ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሶሃቦች ሁሉ በደስታ ሲስቁ አስ-ሲዲቅ ብቻ በአንቀጹ ስለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መሰናበት የሚጠቁም ነገር እንዳለ ስለገባቸው ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሕመም ይጠናባቸው ጀመር፡፡ ዓኢሻ ቤት ሆነው ታስታምማቸው ዘንድ እንዲፈቅዱላቸው ሚስቶቻቸውን ሁሉ
አስፈቀዱ፡፡ ፈቀዱላቸው፡፡ የመጨረሻዎቹ ሰዓታት ሲደርሱ ሶሃቦች ሁሉ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ተሰባስበው ከፍ ባለ ድምፅ ያዝመትሙ ጀመር። ረሱል (ስ.ዐ.ወ) ድምጻቸውን ሰምተው ምን እንደሆኑ ሲጠይቁ በርሳቸውስጋት ገብቷቸው እንደሆነ ተነገራቸው!! ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "ያሉበት ተሽክማችሁ ውሰዱኝ» አሉ፡፡

  እንደደረሱም ሶሃቦችን እንዲህ አሏቸው «እናንተ ሰዎች ሆይ! የኔ ሁኔታ አስፈርቷችኋልን?» ሶሃቦችም "አዎን አንቱ የአላህ መል
ዕክተኛ» በማለት መለሱላቸው እርሳቸውም እንሚከተለው አሏቸው... «እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ
አይደለችም፡፡ ቀጠሮዋችን ሐውድ ዘንድ ነው፡፡ ከዚሁ ሆኜ እያየሁት ይመስለኛል...

----------ኢንሻአላህ ይቀጥላል-----
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ

http://t.me//@arebgendamesjid
158 views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:55:34 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-17-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
175 views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:50:32 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-16-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
177 views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:50:23 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                     ክፍል ዘጠኝ
 
  «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኛ በቀጥታ የመጣነው ፈጅር ለመስገድ ነው በዚህ ሰዓት እንዴት የታመመን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡» በማለት ዕይድ ዑመር መለሱ፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኔ ወደ መስጅድ ለመሄድ ከቤቴ ስወጣ ትላንት ወንድሜ አብዱራህማን ቢን ዐውፍ መታመሙን አስታወስኩ፡፡ የርሱ ቤትና የእኔ ቤት በመስጅዱ መካክል ይገኝ ነበር፡፡ ለሪጅር ሶላት መንቃቱን ስላወቅኩ  አንድ አፍታ ገብቼ ጠየቅሁትና ወደዚህ ለሶላት መጣሁ» አሏቸው፡፡

    ረሱል (ሰዐ,ወ) ቀጠል አደረጉና «ዛሬ ምሽት ከናንተ ውስጥ ሶደቃ የሰጠው ማነው?» ብለው ጠየቁ፡፡ ዑመርም “በዚህ ምሽት ሶደቃ የሰጠነው ማንም ደሃ የለም” ብለው መለሱ፡፡ «አንቱ፡ የአላህ መልዕክተኛ ቢን ዓውፍን ከጠየቅሁ በኋላ ወደ መስጂድ ስገባ ድሃ አገኘሁና በእጄ የተጋገረ ዳቦ ይዤ ስለነበር ለርሱ ሰጠሁት» በማለት አቡበክር ተናገሩ፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “አንተ አቡበክር ዛሬ አንተን በጀነት
አብስሬሃለሁ ይህን ሁሉ ሥራ የሠራ ሰው ጀነት ሊበሰር ይገባዋል፡፡”
ዑመርም ደንገጥ አሉና “አቡበክር ሆይ! በምንም ነገር አንተን ቀድሜህ አላውቅም" አሏቸው።

                   ከባዱ ዘመቻ

   ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ፡- «በተቡክ ዘመቻ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደኛ መጡና ለዘመቻው ግልጋሎት ይውል ዘንድ እንድንወድቅ (እንድንመጸውት) ቅስቀሳ እደረጉልን። ይህ ሀሳብ በጣም ተስማማኝ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ ስለነበረኝ ዛሬ እበበክርን በመብለጥ አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡ ወደ ቤቴ ሄድኩና ካለኝ ገንዘብ ውስጥ ግማሹን ይዤ ተመለስኩና ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ፊት ዘረጋሁት፡፡ እሳቸውም «ለቤተሰቦችህ ምን ያህል
እስቀረህላቸው ብለው ጠየቁኝ። እኔም "ከገንዘቤ ግማሹን ትቼላቸዋለሁ::" አልኳቸው። አቡበክርም(ረ.ዐ) ምንም እንኳ ከዑመር ያነሰ ቢሆንም ቤታቸው ሄደው ገንዘባቸውን ሁሉ አንዲትም ሳያስቀሩ ጠራርገው በማምጣት ነብዩ(ሲ.ዐ.ወ) ፊት ዘረገፉት ነብዩም (ሰዐ,ወ) ለቤተሰቦችህ ምን ያህል አስቀረህላቸው አቡበክር? በማለት ጠየቋቸው:: አበበክርም «ለቤተሰቦቼ ከአላህና ከርሶ በስተቀር ምንም የተውኩላቸው ነገር የለም፡፡"  በማለት መልስ ሰጡ። እኔም እንዲህ አልኩኝ "አቡበክር ሆይ! ወላሂ
ከአሁን በኋላ ካንተ ገር ለመፎካከር አልሞክርም።"  ሃብት ንብረታቸውን በመሉ ለአላህ (ሱ.ወ) ዲን ሲሉ ለሶስት ጊዜያት ያህል የሰጡት ብቸኛ ጀግና አቡበክር አስ-ሲዲቅ ናቸው፡፡

   እስቲ ጥቂት ቆም ብለን ራሳችንን እንጠይቅ! ማነው እስቲ ከኛ
ውስጥ ለአላህ (ሱ.ወ) ብሎ የተቸገሩ ወገኖቹን ለመርዳት ገንዘቡን ሁሉ የሚሰጥ ሰዎች አሁንም ሞልተዋል፡፡ እኔ ራሴ በዐይኔ አንድ በጣም ደካማ ሰው የቦስኒያ ሙስሉሞችን ለመርዳት ራሱ የሚጠቀምበትን ዊልቸር ሲቸር ተመልክቻለሁ፡፡ አንዲት ሴትም ምንም ነገር ስላልነበራት ሙስሊሞችን ለመርዳት የራሷን ጌጣ ጌጦች ስትሰጥ አይቻለሁ፡፡ በዚህ ኡማ ውስጥ የአቡበክርን ዓርአያነት የሚከተል ሰው ሞልቶናል፡፡ ይህ ዓይነቱ ድንቅ ዓርአያነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንመኛለን፡፡

  አቡበክር ገንዘባቸውን ሁሉ ለአላህ (ሱ.ወ) ሲሉ ሶስት ጊዜያት
ያህል መጽውተዋል ብለናል፡፡ እነርሱም፡-
-አንዲት ሚስኪን ሴት ከባርነት ነጻ ሲያወጡ፣
- ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና ሲሰደዱና
- አሁን እንዳልነው በተቡክ ዘመቻ ወቅት ናቸው፡፡

          ለአላህህ (ሱ.ወ) የነበራቸው ፍራቻና ክብር

    ከዕለታት አንድ ቀን የአስ-ሲዲቅ አገልጋይ ለአቡበክር ምግብ
ያቀርብላቸዋል፡፡ አቡበክርም ትንሽ ቀመስ ያደርጉለታል፡፡ አንድ ምግብ ሲቀርብላቸው የምግቡ አመጣጥ ከየት እንደሆነ የመጠየቅ ልምድ ነበራቸው፡፡ በዚህም መሠረት አገልጋያቸውን የምግቡን ምንጭ ይጠይቁታል፡፡ ‹‹ሙስሊም ከመሆኔ በፊት ለስዎች እጠነቁል ነበር፡፡›› በወቅቱ አንድ የጠነቆልኩለት ሰው የነበረበትን ዕዳ ኣሁን ስለከፈለኝ በዚሁ ገንዘብ ነው ይህን ምግብ የገዛሁት ይላቸዋል፡፡

   አቡበክርም በጣም ተደናግጠው «አጥፍተኸኝ ነበር›› ይሉና
ጣታቸውን ወደ ጉሮሮዋቸው ሰድደው የገባውን ለማውጣት ከራሳቸው ጋር መታገል ይጀምራሉ፡፡ ይህን የተመለከቱ ሰዎች በላዩ ላይ በብዛት ውሃ ጠጥተው ካልሆነ ሊወጣሳቸው እንደማይችል ይነግሯቸዋል። ውሃ አምጣልኝ ብለው ያዛሉ፡፡ የመጣላቸውን ውሃ በደንብ ከጠጡ በኋላ እንዲያስታውካቸው በማድረግ የቀመሱትን ጥቂት ጉርሻ ነቅለው ያወጡታል፡፡ ሁኔታውን የሚመለከቱት ሰዎች ‹‹አላህ ይዘንሎት! ትንሽ ነበርች›› ይሏቸዋል፡፡ እርሳቸውም «ወላሂ  ነፍስህ ካልወጣች በስተቀር አትወጣም ነበር ብባል እንኳ ጎልገዬ አወጣት ነበር” ይላሉ፡፡

              አስገራሚ ትህትናቸው

በመዲና ከተማ ውስጥ ባጋደለ ደሳሳ ጎጆ ውስጥ የምትኖር
አንዲት ድሃ አሮጊት ሴትዮ ነበረች፡፡ አቡበክር አስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) በየሳምንቱ ወደ ቤቷ እየሄዱ ቤቱን አጽድተውላት ይመለሱ ነበር፡፡

     ከዕለታት አንድ ቀን ሰይድ ዑመር (ረ.ዐ) የባልቴቷን ደካማነት ይሰሙና ሊጠይቁዋት ቢሄዱ ቤቷ ጥርት ባለ ንጽህና መያዙን ያዩና እንዲህ አድርጎ የሚያጸዳላት ማን እንደሆነ ይጠይቋቸዋል፡፡ ሴትየዋም ማንነቱን የማያውቁት አንድ ሰው በየሳምንቱ እየመጣ እንደሚያጸዳላቸው ይነግሯቸዋል፡፡

    ሰይድ ዑመርም የዚህን ደግ ሰው ማንነት ማወቅ ይኖርብኛል
በማለት በሳምንቱ ተደብቀው መጠባበቅ ይጀምራሉ፡፡ ዑመር(ረ.ዐ) ሁኔታውን እንዲህ ይተርካሉ፡፡ «አቡበክር(ረ.ዐ) መጥተው ቤቱን አንኳኩ፡፡ በሩ እንደተከፈተላቸው አሮጊቷን ወደ ውጪ ደግፈው አወጧቸውና ቤቱን ካጸዱ በኋላ ሴትየዋን ወደ ነበሩበት መልስው ወዲያው በመውጣት ወደ መጡበት አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡››

  ኧረ ለመሆኑ ! እስኪ ማነው ከእኛ ውስጥ ሃቃቸው የማያልቀውን
እናት አባቱን እንኳ እንዲህ አድርጎ የሚያገለግለውና የሚያግዘው?
ራሳችንን መጠየቅ አለብን፡፡

       ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስስል ሲዲቅ የነበራቸው ውዴታ

  አንድ ቀን ሶሀባዎች በተሰበሰቡበት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መስጂድ ገቡና ‹‹አቡበክርስ የታለ?›› ሲሉ ጠየቁ፡፡ አቡበክር ቆም አሉ "ና አጠገቤ ሁን” አሏቸው፡፡ “ዑመርስ የት አለ” ሲሉ አስከተሉ፡፡ እርሳቸውም ቆም ሲሉ ‹‹ና አጠገቤ ሁን›› አሉና የሁለቱንም ሶሀቦች እጅ ይዘው ከፍ
በማድረግ እንዲህ አሉ “በዕለተ ትንሳኤ ልክ እንደዚህ ነው
የምንቀሰቀሰው፡፡”

   ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ከሰው ሁሉ ማንን ይበልጥ እንደሚወዱ ሲጠየቁ ‹‹ዓኢሻን› አሉ፡፡ ከወንዶችስ ሲባሉ ‹‹አባቷን አቡበክርን›› አሉና እንዲህአሉ «አቡበክር ሆይ! በዋሻው ውስጥ ጓደኛዬ እንደነበርከው ሁሉ የጀነትን መጠጥ (ሐውድ) ሳከፋፍልም የቅርብ ጓደኛዬ ትሆናለህ፡፡»

  ከዕለታት አንድ ቀን ሰይድ ዑመር በአንዲት ንግግር አቡበክርን ያኮርፏቸውና ጥለዋቸው ይሄዳሉ፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) ከኋላ እየተከተሉ "ዑመር እባክህ አትቆጣ ይቅር በለኝ” ቢሏቸው ዑመር(ረ.ዐ) ዝም ብለዋቸው ሄዱ፡፡

  ሰይድ አቡበክር(ረ.ዐ) ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው «ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም ዑመር ትንሽ ቆይተው...
http://t.me//@arebgendamesjid
--------ኢንሻአላህ ይቀጥላል.......

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
171 views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:07:00 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-15-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
358 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:06:51 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                ክፍል ስምንት

   ከርሱ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የሌለ በሆነው አላህ
ምዬ መናገር እችላለሁ፡፡ በዚህ ዓለም ውስጥ ከነቢያት በስተቀር እንደ አቡበክር ያለ ታላቅ ሰው እስከ አሁን ድረስ አልተፈጠረም።

    ብዙ ሙስሊም ወጣቶች ታላላቅ አድርገን የምንቆጥራቸው
ምን አይነት ሰዎችን ነው? እስኪ የአቡበክርን ታሪክ ለመመርመር ጥረት እናድርግ፡፡ ከተራራ የገዘፈ ታላቅነት ጎልቶ ይታየናል። የአስ-ሲዲቅን ሕይወት እንመርምር፡፡

           እስክጠግብ ድረስ እርሳቸው ጠጡ!

      አቡበክር አስ-ሲዲቅ ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ረዘም ላለ ጊዜ በዋሻው ተሸሽገው ቆዩ፡፡ ሁለቱንም ረሃብና ጥማት ያሰቃያቸው ጀመር፡፡ አንድ እረኛ ከዋሻው ወዲያ ማዶ ሲያልፍ ተመለከቱ፡፡ ጥቂት ወተት ካለው ይሰጣቸው ዘንድ ለመጠየቅ አቡበክር ወጣ አሉ፡፡ መጠነኛ ወተት ከእረኛው አገኙ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲጠጡ አደረጉ፡፡ አቡበክር ይህን ሁኔታ በተመስጦ ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ፦

  “ወተቱን እኔ እስክረካና እስክጠግብ ድረስ እርሳቸው ጠጡ፡፡” እንዴት ያለው ፍቅር ነው! የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እርካታ የርሳቸው እርካታ ሆነ፡፡ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መጥገብ ለርሳቸውም ጥጋብ ሆነ፡፡ እንዲህ ያለ ፍቅር ታይቶም አይታወቅም! ከዚህ በኋላ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና ወዳጃቸው ጉዙዋቸውን ወደ መዲና አቀኑ፡፡ አቡበክር በአካባቢው ታዋቂ ነጋዴ ስለነበሩ በየመንገዱ ያገኙዋቸው ሰዎች ሰላምታ
ያቀርቡላቸዋል።

    ስለ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ማንነትም ይጠይቋቸው ነበር። አንዱን ሰላም ሲሉት ይህ ሰው ማነው አቡበክር በማለት ይጠይቃቸዋል ይህ መንገድ የሚመራኝ ሰው ነው በማለት ይመልሳሉ። ጠያቂው ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡበክር መንገድ የሚመሩት ሰው እንደሆነ እንዲገምት አድርገዋል። በእርግጥ አቡበክርን የሐቅ የእውነትና የጀነት መንገድ ይመሯቸው የነበሩት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ናቸው። ዑመር ቢን አል-ኸጣብ የአቡበክር መዓዛ እንደሚስክ ሽቶ ያውዳል ይሉ ነበር፡፡

                     እኔ ተራ ሰው ነኝ
           እርሶ ግን የዚህ ዲን ዓርማ ነዎት!

አቡበክር ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና አብረው በመጓዝ ላይ
እያሉ አንዴ ወደፊት አንዴ ደግሞ ወደኋላ ቆይተው ደግሞ ከግራና
ከቀኝ እየሆኑ ያጅቧቸዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) “ምን ሆነህ ነውአቡበክር” ይሏቸዋል። አቡበክርም “መጠበቅ እንዳለብኝ ሳስታውስ ከፊት እሆናለሁ። ከዛም የሚያሳድዱዎትን ሳስታውስ ከኋላ እሆናለሁ ከዚያም በግራዎ በኩል አንድ ነገር እንዳይጎዳዎ እልና በግራዎ እሆናልሁ፡፡" በቀኝ በኩልም ምንም ነገር እንዳያገኝዎ እሰጋና በስተቀኝ እሆናሉ፡፡ ‹‹አቡበክር ይህን ያህል ትወደኛለህ እንዴ?›› ይላሉ፡፡ ‹‹እጀግ በጣም ነው እንጂ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹በእኔ ቦታ ሆነህ ለመሞት ትፈልጋለህ ማለት ነው?›› ብለው ይጠይቃሉ ‹‹አዎና እኔ ብሞት እኮ ተራ ሰው ነኝ፡፡ እርሶ ግን የማይገኙ የዚህ ዲን አርማ ነዎት፡፡››

            አምሳያ የሌለው ሥነ-ምግባር

   አቡበክር አስ-ሲዲቅ ከላይ በተጠቀሰው መልኩ እያደረጉ መዲና
እስኪገቡ ድረስ አብረዋቸው ተጓዙ፡፡ ወደ መዲና ሲቃረቡ የመዲና ሰዎች (አንሷሮች) እየጠበቋቸው ነበር፡፡ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) በመልክ ለይተው አያውቋቸውም። አቡበክር ለጥበቃ ከፊት ከፊት ይጓዙ ስለ ነበር አንሷሮች ሁሉ እርሳቸው መስለዋቸው ነበርና የተጫነበትን ግመል ይዘውላቸው ወደፊት ይመሩ ጀመር፡፡ ይሄን ጊዜ አቡበክር ሁኔታው ይገባቸውና ኩታቸውን ያወልቁና ጥላ ይሆናቸው ዘንድ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ይከልሉበታል፡፡ አንሳሮችም ወዲያው ነገሩ ይገባቸውና የረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ግመል መሳብ ይጀምራሉ።

              የውመል ፉርቃን

       ጊዜው ሄዶ ሙስሊሞች መዲና ላይ መሠብሰብ ጀመሩ። ታላቁ የበድር ጦርነት ተከሰተ፡፡ የአስ-ሲዲቅ ልጅ ዐብዱረህማን በወቅቱ ገና አልሰለመም ነበር፡፡ በውጊያው ዕለት ሰይፉን ከአፎቱ መዘዘና "ማነውየሚገጥመኝ?›› ብሎ ፎከረ፡፡ አቡበክር(ረ.ዐ) ተነሱና ««የአላህ መልዕክተኛ ሆይ እኔ እገጥመዋለሁ›› አሉ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) "ተወው እኔ እበቃዋለሁ" ብለው ተነሱ፡፡ ዐብዱረህማን ቢን አቡበክር ከሰለሙ በኋላ ለአባታቸው እንዲህ አሏቸው “ያኔ ካንተ ጋር ላለመግጠም ብዬ እየተደበቅሁ ነበር፡፡
አቡበክርም(ረ.ዐ) ‹‹ወላሂ ያኔ ባገኝህ ኖሮ አልምርህም ነበር›› አሉት፡፡

    አቡበክር ሰውነታቸው ለስላሳና ክብደታቸው ቀላል ቢሆንም
የቀልባቸው ጥንካሬ ግን ድንቅ ነበር፡፡ የአላህ (ሱ.ወ) ውሳኔ እርሳቸውን የመሰሉ ሰዎች በዓርአያነት ይከተሏቸው ዘንድ ገርና ለስላሳ ሆነው ተፈጠሩ፡፡ ህይወታቸውና ገንዘባቸው የአላህ (ሱ.ወ) ዲን የበላይ ይሆንዘንድ የማያወላውሉ ሰዎች አስ-ሲዲቅን በዓርአያነት መከተል ይኖርባቸዋል፡፡ እርሳቸውን ሞዴል ማድርግ አለባቸው፡፡

    የበድርን ውጊያ አቡበክር ጀብድ በተሞላበት ሁኔታ ነው ያሳለፉት፡፡ በወቅቱ ሶሃባዎች ከከህዲያኖች ይከላከልላቸው ዘንድ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዙፋን ሠርተውላቸው ነበር፡፡ ይህን ሠርተው ካበቁ በኋላ ከረሱል (ስ.ዐ.ወ) ጎን ሆኖ የሚከላከል ሰው ይመርጡ ጀመር፡፡ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ዓልይ ቢን አቡጣሊብ(ረ.ዐ) ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ ‹‹ይህንኑ ኃላፊነት ለመውጣት ሁላችንም አፈግፍገን ነበር፡፡ አቡበክር ሰይፋቸውን መዘው መጡና ‹‹የረሱልን ዙፋን እኔ እየጠበቅኩ እከላከላለሁ አሉ፡፡ እስከመጨረሻው የውጊያ ሰዓት ድረስም ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሳይለዩ በተከላካይነት ቆዩ፡፡››

   አቡበክር የነበራቸው ወኔ እጅግ ከፍተኛና እንግዳ ነበር፡፡ ለጀነት
በተለይ ደግሞ ለከፍተኛው የፊርደውስ ጀነት የነበራቸው ጉጉት
አስገራሚ ነው፡፡ ይህንን ክስተት እስኪ እናስተውል።

   አንድ ቀን ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሶሃቦቻቸውን (የዕምነት ጓዶቻቸውን)
ሰብስበው ስለጀነት ሰዎች ሁኔታ ይነግሯቸው ነበር፡፡ ‹‹ጀነት ውስጥ የተለያዩ የማዕረግ በሮች አሉ፡፡ እንደየሥራው በየበሩ የሚጠራ ሰው አለ፡፡ የሰላት ሰው በሰላት በር፤ የጾመ ሰው ረያን በሚባል በር፤ ሙጃሂድ ሆነ የሞተ ሰው የጂሀድ በር በሚባለው በኩል፤ የሶደቃ ሰው የነበረ በሶደቃ በር፣ በሚባለው በኩል እንደየሥራው እየተጠራ ይገባል›› ብለው ነገሯቸው፡፡

የጀነት ጉጉታቸው ወደር ያልነበረው አቡበክር እንዲህ በማለት ጠየቁ... ‹‹አንቱ የአላህ መልዕክተኛ በሁሉም በር እየተጠሩ መግባት የሚቻልበት ሁኔታ አለን?›› ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «እንዴታ አቡበክር አንተ ከእንዲህ ዓይነት ሰዎች እንድትሆን እመኛለሁ፡፡» አሏቸው።

                  ሁለገብ ማንነት

  በአንድ ወቅት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሙስሊሞችን የፈጅር ሶላት ካሰገዷቸው በኋላ ወደ እነርሱ ተቀጣጭተው ተቀመጡና እንደሚከተለው ጥያቂያዎችን አቅረቡ፡፡ «ከናንተ ውስጥ ማነው ለዛሬ ጾምን ነይቶ ያደረው፡፡ ሁሉም ዝም ሲሉ ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) «አንቱ የአላህ መልእክተኛ! እኔ ለመጾም ነይቼ አላደርኩም›› አቡበክር(ረ.ዐ) ቀበል አደረጉና «እኔ ጾምን ነይቼ ነው ያደርኩት» አሉ፡፡ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ጥያቄዎችን እያከታተሉጠየቁ «ከእናንተ ውስጥ ታማሚን የጠየቀ ማነው?» «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኛ በቀጥታ የመጣነው ፈጅር ለመስገድ ነው በዚህ ሰዓት እንዴት የታመመን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡» በማለት ሰይድ ዑመር....
http://t.me//@arebgendamesjid
321 views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:08:48 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-13-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
507 views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:08:38    የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል ስድስት

    ለዚህ ነበር በወቅቱ ወደ እስልምና ገብተው የነበሩ አዳዲስ ሰዎች ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያደረጉትን ይህንን ጉዞ አምኖ ለመቀበል የተሳናቸዉ፡፡ የቁረይሽ ሙሽሪኮችና ባላባቶች ይህንኑ ዜና በሰሙ ጊዜ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ለማሳጣትና ለማዋረድ የማይገኝ እድል ያገኙ ስለመሰላቸው ጮቤ ረገጡ፡፡ ክፍተትን ለስህተት ለመጠቀም ያላቸው አቋም ይገርማል፡፡

    በነገሩ ለመሳለቅና ለማሾፍም ወደ አቡበከር (ረ.ዐ) ዘንድ ሄዱ፡፡
እንደደረሱም ለአል ሲዲቅ እንዲህ አሏቸው፡- "አቡበክር ሆይ! ጓደኛህ የሚዘላብደውን ሰምተሀልን?” ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በኢስራእና ሚዕራጅ ስላደረጉት ጉዞ የተናገሩትን ነገሯቸው፡፡ አቡበከርም(ረ.ዐ) "በእርግጥ እንዲህ ብሏል? አሉ፡፡“አዎ! ብሏል፡፡” አሏቸው፡፡ አቡበከርም (ረ.ዐ) "በእዉነት ይህንን ብሎ ከሆነ እውነትን ተናግሯል።” አሉ፡፡

   ቁረይሾቹም "ይህንን አምነህ ትቀበላለህ?” ሲሉ ደግመው
ጠየቋቸው፡፡ “ከዚህ የበለጠ ነገር ቢናገሩም አምናቸዋለሁ፡፡” ሲሉ
መለሱ..." ወደ እርሳቸው እንሂድ አሉ። ወደ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ
እንደደረሱም ስለ ኢስራእና ሚዕራጅ የተከተለውን ሁሉ በዝርዝር
ነገሯቸው፡፡ አቡበከርም እንዲህ አሉ፡- "እውነት ተናግረዋል! እውነት
ተናግረዋል! እርሶ የአላህ መልክተኛ መሆንዎን እመሰክራለው፡፡”
ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "አቡበከር ሆይ! አንተ እውነተኛ ነህ፡፡” አሏቸው፡፡

       ከማንም የተሻለ ጉርብትና

  የመካ ከሓዲያን በረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እና በተከታዮቻቸው ላይ
የሚያደርሱት ስቃይና ግፍ በጣም እየበረታ ሲመጣ! ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡበከር ወደ ሐበሻ ይሰደዱ ዘንድ ፈቀዱላቸው፡፡ ከቁረይሽ ጎሳዎች ዉስጥ በጣም የተከበረ ሰው የነበረው ኢብኑ ዱግና ይህንን ይሰማና፤ የሚሻለው የርሱ ጎረቤት ሆነው መኖር ከቻሉ ማንም ሊነካቸዉ እንደማይችል ለአቡበክር ይመክራቸዋል፡፡

    ሰይድ አቡበክር በኢብን ዱግና ምክር ይስማማሉ፡፡ አቡበክር (ረ.ዐ) የዚህ ሰውዬ ጎረቤት ሆነው በመኖር ብዙ ጊዜ ቁርኣን እየቀሩ ያለቅሱ ነበር። እንዲህ ሲያደርጉ ሴቶችና ህፃናት ከበዋቸው ያዳምጡ ስለነበር በጣም ይማረኩና ተፅዕኖ ያድርባቸው ነበር፡፡

     ቁረይሾች በዚህ ሁኔታ ብዙም ስላልተደሰቱ፤ ከዚህ ተግባር
እንዲታቀቡ ይነግሯቸው ዘንድ ኢብን ዱግናን ይልኳቸዋል፡፡ ኢብን
ዱግናም በተላኩት መሰረት አቡበክር በቤታቸው ሆነው እንዲቀሩ
ይነግሯቸዋል። አቡበክርም በመንገድ የሚያልፉ ሰዎች እንዲሰሟቸው በሚል በቤታቸው መስኮት አቅጣጫ ሆነው መቅራት ይጀምራሉ፡፡

     የመካ ቁረይሾች ይኸኛው ሁኔታም ቢሆን ስላልተስማማቸው ጎረቤታቸው ወደሆኑት ሰው (ኢብን ዱግና) ስሞታ ያቀርባሉ፡፡ ኢብን ዱዓናም ቁርአኑን መቅራት እንዲያቆሙ ለአቡበክር ይነግሯቸዋል።
አቡበክር ግን ቁርኣን መቅረቱን ማቆሙ በጭራሽ እንደማይችሉ
ይነግሯቸውና እንዲህ ይላሉ፡- "ወላሂ ሰዎች ቁርኣን እንዲሰሙ
ማድረጌን አላቆምም፡፡ ከፈለክ ጉርብትናህ ይቅርብኝ፡፡ ካንተ የተሻለና የበለጠ ጎረቤት አግኝቻለሁ፡፡” (ቁርኣንን ማለታቸው ነው፡፡)

                    ለቅሶ
      አቡበክር አስ-ሲዲቅ ቁርኣን በሰሙ ቁጥር እንባቸውን
አይቆጣጠሩም ነበር፡፡ በጣም ስቅስቅ ብለው ያለቅሳሉ፡፡ በተለይ ሱረቱል ዘልዘላን በቀሩ ቁጥር ማልቀስ የዘውትር ልማዳቸው ነበር፡፡

     ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በመሞቻቸው ዕለት ታመው ነበርና ሶላት
እንዲያሰግዱ አቡበክርን ያዟቸዋል፡፡ ይሄኔ እሜቴ ዓኢሻ (ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ፡- “አንቱ የአላህ መልእክተኛ! አቡበክር እኮ ለስላሳ ስው ነው። ቁርኣን ሲቀራ እምባውን መቆጣጠር ስለማይችል ሰፉዋን ምን እንደሚል መስማት አይችሉም፡፡ ስለዚህ ዑመርን ይዘዟቸው...”

    በአንድ ወቅት ከየመን የመጣ ልዑክ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ
ይመጣና ለእስልምና ቃል ኪዳን (ሙባየዓ) ይገባል፡፡ ልዑኩ ቁርኣን
ኢስማም ያለቅሳል፡፡ ይሄኔ አቡበክር እንዲህ ይላሉ..“ቀልቦቻችን
ሳይደርቁ በፊት እኛም እንዲህ ነበርን፡፡” ወዲያዉም ማልቀስ ይጀምራሉ፡፡

       እስኪ የታላቁን አቡበክር (ረ.ዐ) ሁኔታ ከራሳችን ሁኔታ ጋር
እናነፃፅረው፡፡ ለመሆኑ እኛ አላህን ፈርተን፣ ቁርኣን ሰምተን
ያለቀስነበትን ጊዜ እናስታውሳለን? ለምን ይሆን ቀልባችን እንዲህ
የደረቀው? ለምንስ ይሆን ከዓይናችን እንባ የጠፋው? መጠያየቅ አለብን!

      ስባት ባህሮችን የፈጠረው ኃያሉ አላህ (ሱ.ወ) እርሱን በመፍራት የሚወርድ እንባን ከእኛ መመልከት ይወዳል፡፡ ነገር ግን የእኛ ዐይን ይህን ከማድረግ ሰስቷል፡፡

          በአላህ ቃል ኪዳን ላይ የነበራቸው ፍጹም እምነት

ፋርሶች ሮሞችን በጦርነት ባሸነፉ ጊዜ፤ አላህ(ሱ.ወ)
የሚከተሉትን የቁርኣን አንቀጾች አወረደ....

{ الۤمۤ (1) غُلِبَتِ ٱلرُّومُ (2) فِیۤ أَدۡنَى ٱلۡأَرۡضِ وَهُم مِّنۢ بَعۡدِ غَلَبِهِمۡ سَیَغۡلِبُونَ (3) فِی بِضۡعِ سِنِینَۗ لِلَّهِ ٱلۡأَمۡرُ مِن قَبۡلُ وَمِنۢ بَعۡدُۚ وَیَوۡمَىِٕذࣲ یَفۡرَحُ ٱلۡمُؤۡمِنُونَ (4) بِنَصۡرِ ٱللَّهِۚ یَنصُرُ مَن یَشَاۤءُۖ وَهُوَ ٱلۡعَزِیزُ ٱلرَّحِیمُ (5) }    الروم: ١-٥

አሊፍ ላም፣ ሚም፡፡ ሩም ተሸነፈች። በጣም ቅርብ በኾነችው ምድር፡፡ እነርሱም ከመሸነፋቸው በኋላ በእርግጥ ያሸንፋሉ። በጥቂት ዐመታት ዉስጥ (ያሽንፋሉ) ትእዛዙም በፊትም በኃላም የአላህ ነዉ። በዚያ ቀንም ምእመናን ይደሰታሉ፡፡ በአላህ እርዳታ (ይደሰታሉ) የሚሻውን ሰው ይረዳል እርሱም አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ (አል-ሩም 1-5)

     እነዚህ አናቅጽ ከወረዱ በኋላ አቡበክር አስ-ሲዲቅ በቁረይሽ
ወደ ሙሽሪኮች መሰብሠቢያ እየሄዱ "ሮሞች እንደሚያሸንፏቸው አርግጠኛ ነኝ፡፡” ማለት ጀመሩ፡፡ አቡበክር እንዲህ እርግጠኛ የሆኑት ከላይ የተገለጸዉን የአላህ (ሱ.ወ) ቃል ኪዳን መሠረት አድርገው ነዉ። ኡመያ ኢብን ኸለፍ ይህንን ሲሰማ “እስኪ እዉነተኛ ከሆንክ እንወራረድ” አላቸው፡፡ አቡበክርም ተስማሙ። ኡመያም “መቼ ነው ድል የሚያደርጉት” ሲል አቡበክርን ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም “ከሶስት ዓመታት በኋላ” አሉት።

   ▻▻ኢንሻአላህ ይቀጥላል◅◅
http://t.me//@arebgendamesjid

  
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
371 views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:19:52 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል አምስት

   አቡበክርም (ረ.ዐ) “እሺ ስንት ልክፈልህና ነፃ ትለቀዋለህ?” ብለው ይጠይቃሉ፡፡ “በሰባት ወቄት ወርቅ እሸጥልሃለሁ” ይላል። አቡበክርም (ረ.ዐ) “እሺ እከፍላለሁ” በማለት ይስማማሉ።
ከዚህም ኡመያ ሳቅ ይልና እንዲህ ይላቸዋል፡፡ “ታውቃለህ አቡበክር
ስአራት ወቄት ካልሆነ አልወስድም ብትለኝ ኖሮ እንኳ እሽጥለህ ነበር።” አቡበክርም (ረ.ዐ) መልሰው “ወላሂ መቶ ወቄት ብትጠይቀኝ እንኳ ከፍዬህ እወስደው ነበር፡፡” ይላሉ፡፡ ከዚያ ክፍያውን ፈጸሙና ቢላልን በነፃ ለቀቁት። ከቢላል በኋላም ሕፃናትንና ሴቶችን በገንዘባቸው ነፃ አውጥተዋል።

      አባታቸው ከደካማዎች ይልቅ ይመሰገኑ ዘንድ ጠንከር ያሉትን
ነፃ ቢያስወጡት እንደሚሻል ደጋግመው ቢነግሯቸውም አቡበክር (ረ.ዐ) ግን "ይህን የማደርገው የአላህን (ሱ.ወ) ውዴታ ለማግኘት እንጂ ለሌላ ለምንም አይደለም፡፡” ብለው ይመልሱላቸው ነበር፡፡

   መልካም ድርጊታቸውን ጭቃ ሊቀቡ የተነሱ የመካ ሙሽሪኮች
የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎችን በአቡበክር (ረ.ዐ) ላይ ይነዙ ጀመር፡፡ “ቢላልን ነፃ እንዲወጣ ያደረገው እርሱ እንደሚለው የአላህን ውዴታ ለማግኘት ሳይሆን ከዚህ በፊት ቢላል የዋለለትን ዉለታ ለመመለስ ብሎ ነዉ።" እያሉ ሥራቸውን በማንኳሰስ አንጓጠጡ፡፡ በዚህ ጊዜ አላህ (ሱ.ወ) የሚከተለውን የቁርኣን አናቅጽ አወረደ

{ وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةࣲ تُجۡزَىٰۤ (19) إِلَّا ٱبۡتِغَاۤءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ (20) وَلَسَوۡفَ یَرۡضَىٰ (21) }

“ለአንድ ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡ ግን የታላቅ
ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህን ሠራ)፡፡ ወደፊትም በእርግጥ
ይደሰታል፡፡” (አል-ለይል፡ 19-21)

    ሱረቱል ለይል በውስጧ ያካተተችው መልእክት በአቡበክር (ረ.ዐ) ላይ የተነዛው ሀሰት መሆኑን መግለጫ ነው፡፡ ሃያ አንድ አናቅፅን አካታለች፡፡

              ከሶሐቦች ሁሉ ጀግና
    አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ምንም እንኳ ጉልበታቸው ደካማና
ሰውነታቸው ለስለስ ያለ ቢሆንም በሐቅ ጉዳይ ግን መንፈሳቸው ጠንካራ ነበር። በአላህ(ሱ.ወ) ጉዳይ ማንንም አይፈሩም፡፡

   በአንድ ወቅት ስይድ ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ "ከሰዎች ሁሉ ጀግና
ማንነው? እርሶ ነዎት አሚረል ሙእሚኒን?” ተብለው ሲጠይቁ
የሚከተለውን ምላሽ ሰጡ" የለም! ከሰው ሁሉ ጀግናው አቡበክር አስ-ሲዲቅ ናቸው። በአንድ ወቅት የቁረይሽ ከሃዲዎች ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ከበው ሲያንገላቷቸው ተመለከትኩ፡፡ እኛ ራቅ ብለን ሁኔታውን እንመለከት ነበር፡፡ ለብቻቸው ሆነው ከሃዲዎቹን ገፈታተሯቸው፡፡ ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ዙሪያ ገለል አደረጉዋቸው፡፡ “አላህ ጌታዬ ነው የሚልን ሰው ልትገድሉ ነው እንዴ?” በማለት ተናገሯቸው፡፡ ከሐዲዎቹም ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ተወት አደረጉና አቡበክርን ያዟቸው፡፡ ዑቅበት ቢን አቢ ሙዐጥ የሚባል ከሐዲ መጣና የአቡበክርን (ረ.ዐ) ፊት ይመታ ጀመር፡፡ ፊታቸው እስኪያባብጥ ድረስ በጫማው ደበደባቸው፡፡ አፍንጫቸው
እስኪቀላ ድረስ ፊታቸው አበጠ፡፡ ከፊታቸው ላይም ደም ይፈስ ጀመር፡፡ አቡበክር ሲዲቅ ራሳቸውን ሳቱ፡፡

     ትንሽ ቆይቶም የአቡበክር (ረ.ዐ) ጎሳዎች የሆኑ በኒ ተሚሞች
መጡና ወደ ቤታቸው ይዘዋቸው ሄዱ፡፡ ከመጎዳታቸው ብዛት ከሞት እንደማይተርፉ እርግጠኛ ነበሩ፡፡ ለእናታቸውም 'በሕይወት ከቆየ መግቢው፣ አጠጭውም' ብለዋቸው ሄዱ፡፡ ከዚያም ወደ ዑቅበት ተመልሰው ሄዱና አቡበክር (ረ.ዐ) ከሞት ሊበቀሉት እንደሚችሉ ዝተው ተመለሱ፡፡

    አቡበክር (ረ.ዐ) ከጉዳታቸው ትንሽ መለስ በማለት ዓይናቸውን
እንደከፈቱ ወዲያው የጠየቁት ጥያቄ «ረሱል እንዴት ናቸው?” የሚል ነበር፡፡ በወቅቱ ያልሰለመችው እናታቸው አጠገባቸው ነበረችና አሁንም ታስታውሰዋለህ እንዴ! አለቻቸው... እርሳቸውም "ወላሂ ያሉበትን ሁኔታ አውቄ ነፍሴ እስክትረጋጋ ድረስ እህልም ሆነ ውሃ አልቀምስም” ይላሉ፡፡

    በመቀጠልም "ወደ ኡሙ ጀሚል ፋጢማ ቢንት አል-ኸጣብ
(የሰይድ ዑመር እህት) ዘንድ ሂጅና ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያሉበትን ሁኔታ
ጠይቂያት፡፡” አሏቸው፡፡ የአቡበክር (ረ.ዐ) እናት ወደ ተባሉበት ቦታ
ይሄዳሉ፡፡ ያኔ ቢንት አል-ኸጣብ መስለሟን ደብቃ ትኖር ነበር፡፡
የአቡበክር (ረ.ዐ) እናት ስለ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሁኔታ ይጠይቋታል።
እርሷም እንዲህ ትላለች "ወላሂ! ልጅሽንም ሆነ መሐመድን አላውቅም፡፡ ነገር ግን ደስ ካለሽ ልጅሽን ለመጠየቅ አብሬሽ ልመጣ እችላለሁ፡፡”

     ከዚያም ተከታትለው ወደ አቡበክር (ረ.ዐ) ዘንድ ይሄዳሉ፡፡
አቡበክርም "ፋጢማ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዴት ናቸው?” ሲሉ
ይጠይቋታል፡፡ እርሷም "እኔ ሙሐመድ ማን እንደሆነ አላውቅም፡፡”
ስትል ትመልሳለች፡፡ አቡበክርም ነገሩ ገብቷቸው "አትፍሪ እርሷ እናቴ ነች።” ይሏታል፡፡ ከዚያም “ደህና ናቸው ምንም አልሆኑ፡፡” ትላለች አቡበክርም "ወላሂ! በዓይኔ እስካላየኋቸው ድረስ እህልም ሆነ ውሃ አልቀምስም” ይላሉ፡፡ እናትየውም "እግርህ እስኪሻልህ ድረስ ትንሽ ጠብቅ” ይሏቸዋል፡፡

    እርሳቸውም እግራቸው መራመድ እያቃተውም ቢሆን ብድግ
ብለው በመነሳት ሁለቱም ሴቶች ደግፈዋቸው የአል-አርቀም ቢን አቢ አል-አርቀም ቤት ይደርሳሉ፡፡ በር ሲያንኳኩ ይከፍትላቸዋል፡፡ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) አቡበክርን ሲያዩዋቸው በጣም ያዝኑላችዋል። እቅፍ ያደርጓቸዋል፡፡ አቡበክር የረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ማዘን ሲመለከቱ «የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ወላሂ ከፊቴ በስተቀር ደህና ነኝ ምንም አልሆንኩም» ይላሉ። ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) በጣም አዝነው ዱዓ ያደርጉላቸዋል፡፡

    አቡበክርም እንዲህ ይሏቸዋል፡፡ "አንቱ የአላህ መልዕክተኛ!
እናቴን አላህ ሙስሊም እንዲያደርጋት ዱዓ አድርጉላት፡፡” ነብዩም
(ሰ.ዐ.ወ) "አላህ ሆይ! የአቡበክርን እናት ወደ ቀጥተኛው ጎዳና ምራት” ብለው ዱዓ ያደረጋሉ። የአቡበክር እናትም እዚያው እንደቆሙ "ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፡፡ ሙሐመድም የአላህ መልእክተኛ ናቸው፡፡” በማለት የምስክርነት ቃላቸውን ይሰጣሉ፡፡

       አስ-ሲዲቅ ስለ እስልምና የነበራቸው ድንቅ አቋሞች

   ሰይድ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) በእስልምና ዙሪያ የነበራቸውን
አቋሞች ስናይ ለዲን የነበራቸውን ፍቅር ከፍተኛነት መረዳት እንችላለን፡፡ አስ-ሲዲቅ ሁሉ ነገራቸውን ለዲን የበላይነት ሲሉ
ገብረዋል። ነፍሳቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ቤተሰባቸውን ደማቸውን ይህን ሃይማኖት ለማገልገል ሲሉ ሰጥተዋል፡፡ ለእስልምና የበላይነት ሲሉ ሁለመናቸውን ከፍለዋል፡፡

   ስለ አስ-ሲዲቅ አቋሞች ስንነጋገር ዋነኛው ዓላማችን ሁሉም
ሙእሚን በዓርአያነት እንዲከተላቸው ነው፡፡ አቡበክርን (ረ.ዐ) ተምሳሌት አድርገን ከእስልምና ረገድ ያለብንን ኃላፊነቶች ሁሉ በአግባቡ እንድንወጣ ያግዘናል።

            ዕለተ-አል ኢስራእ ወል ሚዕራጅ

   ምንም ዓይነት ፈጣን የትራንስፖርት አገልግሎት ባልነበረበትና
በማይታወቅበት ዘመን አንድ ሰው አንድ ሙሉ ሌሊት ባልሞላ ጊዜ
ዉስጥ ከመካ ተነስቶ ቁድስ ደርሶ ተመለሰ ተብሎ ቢነገር የሚታመን ነገር አልነበረም ::
398 views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 22:29:21 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል አራት

              የአስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ያሰብዕና ቁልፍ
  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ፡፡ "ከሰዎች ሁሉ በእውነተኛ እምነቱ ወደር የማይገኝለት ስው አቡበክር አስ-ሲዲቅ ነው፡፡” እንዲህም ይላሉ... "ከሰዎች ሁሉ በጽኑ እምነቱ አቻ የማይገኝለት ሰው አቡበክር አስ-ሲዲቅ ነው።”

   ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “የኡማው ኢማን በአንድ መዳፍ፤ የአቡበክር ኢማን ደግሞ በሌላ መዳፍ ሆኖ ቢመዘን የአቡበክር ኢማን ባመዘነ ነበር፡፡” ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) "አቡበክር የበለጣችሁ በሶላትና በፆም ብዛት ሳይሆን በቀልቡ ውስጥ ጸዳል በሆነው ኢማኑ ነው፡፡” ሲሉመስክረዋል፡፡

   የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) የስብዕናቸው ቁልፍ የሆነው ለእውነት - የነበራቸው ፍጹም ውዴታ ነበር፡፡ ለእውነት መስዋእት
ለመሆን ሲሉ እድሜያቸውንም ሆነ ደማቸውን ከመስጠት ለአፍታም አላንገራገሩም፡፡
    አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ሕይወታቸውን ሁሉ ምንም ሳይሰስቱ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የሰጡት የእውነት ሁሉ መገኛ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በመሆናቸው ነበር፡፡
     ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ዝንተ-ዓለማዊው ሕይወት
በተሸጋገሩበት ቅጽበት ሶሀባዎች ሁሉ ተደናግጠው የሚያደርጉትን ሲያጡ ግልጽና ትክክለኛ አቋም የወሰዱት ብቸኛው ሰው አቡበክር (ረ.ዐ) ነበሩ፡፡ የአቡበክርን (ረ.ዐ) ሕይወት ምንጊዜም ቢሆን ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠረው እውነት ብቻ ነበር፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መካ ውስጥ የእውነት ተምሳሌት ሆነው ብቅ ሲሉ አቡበክር (ረ.ዐ) በእጃቸው ያለውን ነገር ሁሉ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)
በመስዋኣትነት አቀረቡ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለሕልፈት ሲበቁም አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) በእውነት መስመር ላይ ጸኑ፡፡

   ዑለማዎች አንድ በጋራ የሚስማሙበት ነገር አለ፡፡ ይኸውም
ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በመቀጠል ለመጀመሪያ ጊዜ ለአላህ (ሱ.ወ) ሱጁድ ያደረጉ(በግንባሩ ተደፍቶ የስገደ) እመቤት ኸዲጃ (ረ.ዐ) ናቸው፡፡ ከወንዶች መጀመሪያ የሰለመው ደግሞ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ናቸው። ከሕፃናት የመጀመሪያው እስልምናን የተቀበለ ደግሞ ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ (ረ.ዐ) ሲሆኑ ከአገልጋይ ደግሞ መጀመሪያ እስልምናን የተቀበሉት ዘይድ ቢን ሐሪስ (ረ.ዐ) ናቸው፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለመጀመሪያ ጊዜ ኣቡበክርን (ረ.ዐ) ወደ እስልምና ሲጋብዟቸው ያለምንም ማመንታት ነበር የተቀበሏቸው፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ይህንኑ አስመልክተው እንዲህ ይሉናል "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም፡፡ አቡበክር ግን ስለ እስልምና ስነግረው ወዲያውኑ ያለማመንታትና ያለማንገራገር ተቀበለኝ፡፡ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ ነው በማለት እዚያው መሰከረ፡፡”

  ሰይድ አቡበክር (ረ.ዐ) ወደ እስልምና ጥሪ ሲደረግላቸው
ወዲያውኑና ያለማመንታት የተቀበሉት እንዲሁ በስሜትና በዘፈቀደ
ኣልነበረም፡፡ ምንም ዓይነት ራዕይ ሳይኖራቸው ቀርቶም አይደለም፡፡
ይልቁንም ሐቅ የተባለን ነገር ወዲያውኑ የመቀበልና የማመን ቋሚ
ባህሪ ስለነበራቸው ነው። የእስልምናን እውነት ከተቀበሉበት ዕለት
አንስቶ የብርሃን ፀዳል ቀልባቸውን ይሞላ ጀመር፡፡
እዚህ ቦታ ላይ ለአፍታ ቆም ብለን በማስተዋል ከእኝህ ታላቅ
ሰው መማር ይኖርብናል። እስልምና እውነት መሆኑን አምነን
እስከተቀበልን ድረስ፤ ሁለመናችንን በእስልምና ጥላ ሥር ማኖር
ይገባናል፡፡ አቡበክርን (ረ.ዐ) ተምሳሌት ማድረግ ይኖርብናል፡፡

   ከላይ እንደተጠቀሰው አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) እኛን የበለጡን በሶላት ወይም በዖም ብዛት ሳይሆን የእውነትን ብርሃን ሲመለከቱ በዚያ ውስጥ ተጠቅልለው ለመኖር አንዳችም ባለማመንታታቸው ነው። ነፍሳቸውን፣ ሃብታቸውን፣ ጊዜያቸውን ሁሉ ለእውነት ሰውተዋል፡፡ ለእውነት ሲሉ ደማቸውን ሰጥተዋል፣ ገንዘባቸውን ሁሉ አፍስሰዋል። ኃይላቸውን፣ ችሎታቸውን፣ ልጆቻቸውን ለእውነት ሰጥተዋል።

      ከአቡበክር (ረ.ዐ) ልንማር ከሚገባን ቁም ነገር አንዱ አንድን
እውነት ካወቅን ሕይወታችንን በሙሉ ለዚህ እውነት መስጠትን ነው::

    አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) እስልምናን ሳያወላዱ የተቀበሉት ብዙ ተነግሯቸው ሳይሆን ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጣፋጭ አንደበት በሰሟት ጥቂት ንግግር ነበር፡፡ የእስልምናን መልዕክት ለማስራጨት ባጭር ታጥቀው የተነሱት ወዲያው እንደሰለሙ ነበር፡፡ ለዳዕዋ በተነሱ በመጀመሪያው ሳምንት ውስጥ ጀነት ከተበሰረላቸው (ዐሸረቱል ሙበሸሪን) አስር ሰዎች ውስጥ ስድስቱ በእርሳቸው እጅ ለመስለም በቅተዋል፡፡ እነዚህም፦1. ሰዐድ ቢን አቢ ወቃስ 2.ዙበይር ቢን አል-ዓዋም 3. ጦልሐ ቢን 4. አቡ ዑበይዳህ ቢን አል-ጀራህ 5. ዐብዱራህማን ቢን ዐውፍ 6. ዑስማን ቢን ዓፋን ናቸው፡፡
    እነዚህ ሁሉ ዕንቁዎች በአቡበክር (ረ.ዐ) አማካኝነት የሰለሙት
በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በዚህ ወቅት አስ-ሲዲቅ ስለ
እስልምና ያውቁ የነበረው ጥቂት ነገር ብቻ ነበር።

   ከዚህ አንፃር እስኪ የእኛን ሁኔታ እንገምግመው፡፡ ስለ እስልምና
ብዙ እናውቃለን፡፡ በእኛና በአቡበክር (ረ.ዐ) መካከል ያለው ልዩነት አንድ ነው፡፡ ይኸውም እርሳቸው እውነትን አወቁ ወዲያውኑ ጥቅልል ብለው ለእውነት ብቻ መኖር ጀመሩ፡፡ እኛ ግን እውነትን በብዙ አቅጣጫ አውቀናል፡፡ ለእውነት ለመኖር ግን ዝግጁዎች አይደለንም፡፡ እውነትን አውቀን ለእውነት ብቻ ለመኖር ካልቻልን በእውነት ስህተተኞች ነን።

   አቡበክር (ረ.ዐ) እውነትን አወቁ፡፡ ስሜታቸው ለእውነት ተማረከ።
ለእውነትም ሌትተቀን ሠሩ፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ስድስት ዕንቁዎች
ሙስሊም እንዲሆኑ ምክንያት የሆኑት አቡበክር (ረ.ዐ) ናቸው። እነዚህ ሰዎች የሠሯቸው መልካም ሥራዎች ሁሉ (የነርሱ ምንም ሳይጓደል) ለአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ነው የሚመዘገቡት፡፡ ያደረጉት ዒባዳ፣ ጂሐድ፣ ምጽዋት፣ ዳዕዋ... ሁሉ ምንዳው ለአስሲዲቅ (ረ.ዐ) ነው፡፡

    አቡ ዑበይዳ ቢን አል-ጀራህ ሻምን ሰዐድ ቢን አቢ ወቃስ ደግሞ
ኢራቅን የከፈቱና ያቀኑ ናቸው፡፡ የፋርስንም ቅኝ አገዛዝ ያንኮታኮቱ፡
ናቸው፡፡

    በአቡበክር (ረ.ዐ) እጅ የሰለሙት እጅግ በርካታ ሰዎች ናቸው።
ከእነዚህም ውስጥ አል-አርቀም ቢን አቢ አርቀም፣ ዑስማን ቢን መዝዑን ሊጠቀሱ ይችላሉ። ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በባሪያ ፍንገላ ሥር የነበሩ ብዙ ሰዎች በአቡበክር (ረ.ዐ) ገንዘብ ነፃ ሊወጡ ችለዋል። መጀመሪያ ነፃ የወጡት ሰባት ሰዎች ናቸው። ከነዚህ ውስጥ ቢላል ቢን ረባህ(ረ.ዐ) የመጀመሪያው ነው፡፡

  የቢላል ገዢ ኡመያ ቢን ኸለፍ ይሰኛል። በመስለሙ ምክንያት
ቢላልን ይቀጣውና ያስቃየው ነበር፡፡ አንድ ቀን ቢላልን እያሰቃየው ሳለ አቡበክር (ረ.ዐ) በአጠገባቸው ሲያልፉ ይህንን ይመለከቱና ለኡመያ እንዲህ ይሉታል። “ይህ ምስኪን አያሳዝንህም?" ኡመያም “አንተ እዘንለት” ሲል ይመልሳል፡፡ አቡበክርም (ረ.ዐ) “እሺ ስንት ልክፈልህና ነፃ ትለቀዋለህ?” ብለው ይጠይቃሉ፡፡ 

----------ኢንሻ አላህ ይቀጥላል--------------

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
http://t.me//@arebgendamesjid
89 views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ