2022-12-16 20:49:19
እለቱን በትውስታ part 1
እለቱ 2018 ነው፤የሩስያው አለም ዋንጫ ከ32 ሀገራት 16ቱን አለም ዋንጫው ቀንሷል። አለም ዋንጫው ሩስያን ፣ጃፓንን ፣ስፔንን ፣ኡራጋይን ፣ፈረንሳይን ፣ሜክሲኮን ፣አርጀንቲናን ፣ቤልጅየምን ፣እንግሊዝን ፣ኮሎምቢያ ፣ስዊዘርላንድ ፣ስዊድን ፣ዴንማርክ ፣ክሮሽያ ፣ብራዚል ፣ ፖርቹጋል 16ቱ የቀሩት ሀገራት ናቸው።
የ2018ቱ አለም ዋንጫ ጨዋታ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ አርጀንቲናን ከ ፈረንሳይ አገናኝቷል። ጨዋታው እንደ ፈረንጆቹ Jun 30, 2018 ላይ ቀጠሮ ተይዞለት በቀጠሮው ሊደረግ ነው። ስታዲየሙ በደጋፊዎች ተሞልቷል። አርጀንቲና ከ ፈረንሳይ።
ሁለቱ ሀገራት ለ12ኛ ግዜ መገናኘታቸው ነበር፤ አርጀንቲና በሰአቱ በአለም ዋንጫው በተጋጣሚያቸው ላይ ቢያንስ 3 ግቦችን አስቆጥረው ነው የመጡት። ይህ ደግሞ ከ1986 በኋላ ሲሆን ለመጀመሪያ ግዜ ነበር።
ፈረንሳይ በበኩሏ በ1978 በአርጀንቲና ከተሸነፈች በኋላ ከደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጋር ያደረገቻቸው ያለፉትን ዘጠኝ ጨዋታዎች አልተሸነፈችም።
ማን ያሸንፋል ፈረንሳይ ወይስ አርጀንቲና?
ጨዋታው ሊጀመር ነው
በፈረንሳይ በኩል ሎሪስ በግብ ጠባቂ ፣ፓቫርድ፣ቫራን፣ኡምቲቲ፣ኸርናንዴዝን በተከላካይ ፖግባ እና ኮንቴ በተከላካይ አማካኝ ምባፔ፣ ግሬዝማን እና ማቱዊዲ በመሀል ከፊት ጅሩድን በማሰለፍ በ4-2-3-1 አሰላለፍ ወደ ሜዳ ገቡ ።
አርጀንቲና በበኩሏ አርማኒን በግብ ጠባቂነት፤ታግሊፊኮ፣ሮጆ፣ኦታመንዲ እና ማሼራኖን በተከላካይ ቦታ፤ ባኔጋ፣ ማሼራኖ፣ፔሬዝ በመሀል፤ዲማሪያ ሜሲ እና ፓቮን በአጥቂ ቦታ በ4-3-3 አሰላለፍ ገቡ።
ጨዋታው በካዛን አሬና ስታዲየም ልክ 10:00 ሲል በአርጀንቲናዊው ዳኛ ኔስተር ፒታና አስጀመሩት። ስታዲየሙ በጩኸት ተናጋ ግማሹ አርጀንቲና ግማሹ ፈረንሳይ ይላል...
171 viewsedited 17:49